am_tw/bible/names/greek.md

1.5 KiB

ግሪክ፣ ግሪካዊ፣ የግሪክ ባሕል

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ግሪክኛ በግሪክና በመላው የሮም መንግሥት ብዛት መግባቢያ ቋንቋ ነበር፤ የመጀመሪያው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት በግሪክኛ ነበር።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንዳንዴ አይሁድ ያልሆነ ሰውን በአጠቃላይ ለሚመለከት “ግሪክ” የተሰኘው ቃል ጥቅም ላይ ይውል ነበር። ይህም በዚያ ዘመን ሮም መንግሥት ግዛት ውስጥ የነበሩ አብዛኞቹ አይሁድ ያልሆኑ ሰዎች የተለያዩ አገር ሰዎች ቢሆኑ እንኳ ግሪክኛ ይናገሩ ስለ ነበር ነው። ለዚህ ምሳሌ የምትሆነን ማርቆስ 7 ላይ የተጠቀሰችው ሴርፊኒቃዊት ሴት ናት።
  • አይሁድ ያልሆነ ሰውን አስመልክቶ በዚህ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “ግሪክ” የሚለውን፣ “አሕዛብ” አይሁድ በግሪክ ባሕል ውስጥ ተወልደው ያደጉና ግሪክኛ ይናገሩ የነበሩ አይሁድ ናቸው። አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጕሞች “ግሪክ” የሚለውን የግሪክን ባሕል የተቀበለ በማለት ተርጉመዋል። ይህም ዕብራይስጥን ብቻ የሚናገሩ አይሁድ፣ “ዕብራውያን” ተብለው እንደሚጠሩት ማለት ነው።