ሔዋን
ይህ የመጀመሪያዋ ሴት ስም ነበር። የስሟ ትርጉም፣ “ሕይወት” ወይም፣ “ሕያው” ማለት ነው።
- እግዚአብሔር ሔዋንን የፈጠራት ከአዳም ጎድን ከወሰደው አጥንት ነበር።
- ሔዋን የተፈጠረችው የአዳም “ረዳት” እንድትሆን ነው። እግዚአብሔር በሰጠው ሥራ እርሱን ለመርዳት ከአዳም ጎን ትሆናለች።
- ሔዋን በእባቡ (ሰይጣን)ተፈተነች፣ እንዳይበሉ እግዚአብሔር የከለከለውን ፍሬ በመብላት የመጀመሪያውን ኀጢአት ፈጸመች።