am_tw/bible/names/eve.md

682 B

ሔዋን

ይህ የመጀመሪያዋ ሴት ስም ነበር። የስሟ ትርጉም፣ “ሕይወት” ወይም፣ “ሕያው” ማለት ነው።

  • እግዚአብሔር ሔዋንን የፈጠራት ከአዳም ጎድን ከወሰደው አጥንት ነበር።
  • ሔዋን የተፈጠረችው የአዳም “ረዳት” እንድትሆን ነው። እግዚአብሔር በሰጠው ሥራ እርሱን ለመርዳት ከአዳም ጎን ትሆናለች።
  • ሔዋን በእባቡ (ሰይጣን)ተፈተነች፣ እንዳይበሉ እግዚአብሔር የከለከለውን ፍሬ በመብላት የመጀመሪያውን ኀጢአት ፈጸመች።