am_tw/bible/names/ephesus.md

1.0 KiB

ኤፌሶን

ኤፌሶን በአሁኑ ዘመን ቱርክ በምትባለው አገር ምዕራባዊ ባሕር ዳርቻ የነበረች ጥንታዊ የግሪክ ከተማ ነበረች።

  • በጥንት ክርስቲያኖች ዘመን ኤፌሶን በዚያ ጊዜ ትንሿ የሮም አውራጃ የነበረችው እስያ ዋና ከተማ ነበረች።
  • ከነበረችበት ቦታ አምቺነት የተነሣ ይቺ ከተማ የንግድና የጉዞ ማዕከል ነበረች።
  • የአርጤምስ (ዳያና) ጣዖትን ለማምለክ የተሠራው ታዋቂ የአረማውያን ቤተ መቅደስ ይገኝ የነበረው በአፌሶን ነበር።
  • ጳውሎስ ከሁለት ዓመት የበለጠ በአፌሶን እየኖረ አገለገለ፤ በኋላም እዚያ የነበሩ አማኞችን እንዲያገለግል ጢሞቴዎስን ሾመ።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ያለው የአፌሶን መልእክት ጳውሎስ በአፌሶን ለነበሩ አማኞች የጻፈው ነው።