am_tw/bible/names/engedi.md

762 B

ዓይንጋዲ

ዓይንጋዲ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምሥራቅ ይሁዳ ምድረ በዳ ላይ የምትገኝ ከተማ ስማ ነው።

  • ዓይንጋዲ የሚገኘው ከጨው ባሕር ምዕራባዊ ዳርቻ ላይ ነበር።
  • የስሙ ከፊል፣ “ምንጭ” ማለት ሲሆን ከከተማው ወደ ባሕሩ የሚያልፈውን የውሃ ምንጭ ለማመልከት ይሆናል።
  • ዓይጋንዲ በሚያማምሩ የወይን እርሻዎቹና ምናልባትም ያለሟቋረጥ ከሚፈሰው ምንጭ የተነሣ ሌሎች ለም ቦታዎቹ ይታወቃል።
  • በዓይጋንዲ ንጉሥ ሳኦል ባሳደደው ጊዜ ዳዊት ሸሽቶ የተደበቀበት ዋሻ (ምሽግ) ነበር።