am_tw/bible/names/baal.md

1.4 KiB

በኣል

“በኣል” ፦ “ጌታ” ወይም፥ “አለቃ” ማለት ሲሆን፥ ከነዓናውያን ከሚያመልኳቸው ዋነኞቹ ጣዖቶች የአንዱ ስም ነበር።

  • ከስማቸው ጋር፥ “በኣል” የሚል ስም የተያያዘ ሌሎች የአካባቢው ጣዖቶችም ነበሩ፤ ለምሳሌ “በኣል ጲኦር” አንዳንዴ እነዚህ ጣዖቶች ሁሉ በአንድነት፥ “በኣሎች” ተብለው ይጠሩ ነበር።
  • አንዳንድ ሰዎች፥ “በኣል” የሚል ቃል የተጨመረበት ስም ነበራቸው
  • የበኣል አምልኮ ሕፃናትን መሥዋዕት ማቅረብንና በአመንዝራዎች መጠቀምን የመሳሰሉ መጥፎ ተግባሮችን ይጨምራል
  • በታሪካቸው ውስጥ በአንዳንድ ወቅቶች በዙሪያቸው የነበሩ አረማውያን ሕዝቦችን ምሳሌ በመከተል እስራኤላውያንም በከፍተኛ ደረጃ በኣልን አምልከው ነበር
  • በንጉሥ አክዓብ ዘመን በኣል ሐሰት እንደሆነና እውነተኛው አምላክ ያህዌ ብቻ መሆኑን ለሕዝቡ ለማሳየት የእግዚአብሔር ነብዩ ኤልያስ አንድ ፈተና አቅርቦ ነበር፥ ከዚህም የተነሣ የበኣል ነብያት በሞት ተቀጡ፤ ሕዝቡም እንደገና ያህዌን ማምለክ ጀመሩ።