am_tw/bible/names/absalom.md

1.1 KiB

አቤሴሎም

አቤሴሎም የዳዊት ሦስተኛ ወንድ ልጅ ነበር። በቁንጅናውና በቁመናው እንዲሁም በጣም ቅብጥብጥ በመሆኑ ይታወቃል።

  • የአቤሴሎም እህት ትዕማር ከፊል ወንድሟ በመሆኑ በአምኖን በተደፈረች ጊዜ አቤሴሎም አምኖንን ለመግደል ዕቅድ አወጣ።
  • አምኖንን ከገደለ በኋላ አቤሴሎም የእናቱ የመዓካ አገር ወደ ሆነው ወደ ጌሹር አካባቢ በመኮብለል በዚያ ሦስት ዓመት ቆየ።ከዚያም ተመልሶ ወደ ኢየሩሳሌም እንደመጣ ንጉሥ ዳዊት መልዕክተኞች ላከ ። ይሁን እንጂ ለሁለት ዓመት ያህል አቤሴሎም እፊቱ እንዲቀርብ አልፈቀደም ነበር።
  • አቤሴሎም አንዳንድ ሰዎችን ዳዊት ላይ አነሣሣ፤እርሱ ላይ ዐመፅ አስነሣ።
  • የዳዊት ሰራዊት ከአቤሴሎም ጋር ተዋግቶ ገደለው። እንዲህ በመሆኑ ዳዊት በጣም አዘነ።