am_tw/bible/kt/works.md

1.4 KiB

ሥራዎች፣ ተግባሮች፣ ሥራ፣ ተግባር

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ሥራዎች”፣ “ተግባሮች” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ የዋሉት እግዚአብሔር ወይም ሰዎች ያደረጉትን በአጠቃላይ ለማሳየት ነው።

  • “ሥራ” ሌሎችን ለማገልገል የተከናወነ ማንኛውንም ነገር ያመለክታል።
  • “የእግዚአብሔር ሥራዎች” እና፣ “የእጆቹ ሥራ” የተሰኙት ዓለምን መፍጠሩን፣ ኀጢአተኞችን ማዳኑን፣ ለፍጥረት ሁሉ የሚያስፈልገውን መስጠቱንና አጽናፈ ዓለሙን አጽንቶ መያዝን ጨምሮ እርሱ ያደረገውን ሁሉ የሚያካትት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው።
  • የሰው ሥራ ወይም ተግባር መልካም ወይም ክፉ ሊሆን ይችላል።
  • አማኞች መልካም ፍሬ እንዲያፈሩ መንፈስ ቅዱስ ያስችላቸዋል፤ ይህም፣ “መልካም ፍሬ” የሚባለው ነው።
  • ሰዎች የሚድኑት በመልካም ሥራቸው ሳይሆን፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ነው።
  • ሰው የሚሠራው ራሱን ለመርዳት ወይም እግዚአብሔርን ለማገልገል ሊሆን ይችላል። እግዚአብሔር አሁንም፣ “እየሠራ” መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል።