am_tw/bible/kt/tabernacle.md

1.7 KiB

መገናኛ ድንኳን

መገናኛ ድንኳን እስራኤላውያን 40 ዓመት በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር የሚያመልኩበት ድንኳን መሰል ነገር ነበር

  • ይህን ሁለት ክፍሎች የነበሩትን ዙሪያው ባለው አደባባይ የተከበበውን ትልቅ ድንኳን እንዴት መሥራት እንዳለባቸው እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ዝርዝር መምሪያዎች ሰጥቷቸዋል
  • እስራኤላውያን ወደ ሌላ ቦታ በተንቀሳቅሱ ጊዜ ሁሉ ካህናቱ የመገናኛውን ድንኳን በማፍረስ እስከ ቀጣዩ ሰፈር ድረስ ይሸከሙታል። ከዚያም አዲሱ ሰፈራቸው መካከል የተክሉታል
  • የመገናኛው ድንኳን ከጨርቅ፣ ከፍየል ጠጉርና ከእንስሳት ቆዳ የተሠሩ መጋረጃዎች በተሰቀሉበት የእንጨት ማዕቀፍ የተሠራ ነበር። ዙሪያው ያለው አደባባይም በሌሎች መጋረጃዎች የተከበበ ነበር
  • የመገናኛው ድንኳን ሁለቱ ክፍሎች ቅድስት (የዕጣኑ መሠዊያ ያለበት) እና ቅድስተ ቅዱሳን (የቃል ኪዳኑ ታቦት ያለበት) ናቸው
  • የመገናኛው ድንኳን አደባባይ ለመሥዋዕት የቀረቡ እንስሳት የሚቃጠሉበት መሠዊያና ለሃይማኖትዊ ሥርዓቱ የሚታጠቡበት ልዩ መታጠቢያ ክፍል ነበረው
  • በኢየሩሳሌም የነበረው የሰሎሞን ቤተ መቅደስ ከተሥራ በኋላ እስራኤላውያን መገናኛው ድንኳን ጥቅም ላይ መዋሉ ቀረ