am_tw/bible/kt/resurrection.md

694 B

ትንሣኤ

“ትንሣኤ” ከሞት በኋላ ተመልሶ ወደ ሕይወት መምጣት ነው።

  • አንድን ሰው ማስነሣት ያንን ሰው እንደ ገና ወደ ሕይወት ማምጣት ማለት ነው። ያን የማድረግ ኀይል ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው።
  • ብዙውን ጊዜ፣ “ትንሣኤ” የሚያመለክተው ከሞት በኋላ ኢየሱስ ወደ ሕይወት መመለሱን ነው።
  • ኢየሱስ፣ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” ሲል፣ እርሱ የትንሣኤ ምንጭ መሆኑንና ሰዎችን መልሶ ወደ ሕይወት የሚያመጣ መሆኑን መናገሩ ነበር።