am_tw/bible/other/trample.md

9 lines
1.1 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# ቤተ መቅደስ
ቤተ መቅደስ እስራኤል ለጸሎትና ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ የሚሰበሰቡበት ዙሪያውን በተከበበ አደባባይ ውስጥ ያለ ሕንፃ ነው። ቤተ መቅደስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ባለው የሞሪያ ተራራ ነበር።
* አብዛኛውን ጊዜ፣ “ቤተ መቅደስ” የሚለው ቃል ዋናውን ሕንፃ የሚከብባትን አደባባዮች ጨምሮ መላውን ሕንፃ ያመለክታል። አንዳንዴ የሚያመለክተው ውስጡ የሚፈጸመውን አምልኮ ሳይሆን ሕንፃውን ብቻ ነው።
* የቤተ መቅደስ ሕንፃ ቅድስትና ቅድስተ ቅዱሳን የሚባሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት።
* ቤተ መቅደሱ የእርሱ ማደሪያ እንደ ሆነ እግዚአብሔር ተናግሯል።
* መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው ከመኖሩ የተነሣ በክርስቶስ ያመኑ ሰዎች “የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ” ተብለው ተጠርተዋል።