am_tq/psa/84/07.md

1.2 KiB

የተባረኩ ሰዎች የሚታዩት የት ነው?

በጽዮን በእግዚአብሔር ፊት ይታያሉ፡፡ [84: 7]

ጸሐፊው ጸሎቱን እንዲሰማው የሚፈልገው ማን ነው?

የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ጸሎቱን እንዲሰማው ይፈልጋል፡፡ [84:8]

ጸሐፊው የሚናገረውን እንዲሰማው የሚፈልገው ማንን ነው?

የያዕቆብ አምላክ የሚናገረውን እንዲሰማው ይፈልጋል፡፡ [84: 8]

ጸሐፊው እግዚአብሔር እንዲጠብቅላቸውና ስለማንስ ግድ እንዲለው ይፈልጋል?

እግዚአብሔር ጋሻቸውን እንዲጠብቅላቸውና ለቀባው ሕዝብ ግድ እንዲለው ይፈልጋል፡፡ [84: 9]

በእግዚአብሔር አደባባይ አንድ ቀን ከምን ይሻላል?

በእግዚአብሔር አደባባይ አንድ ቀን በሌላ ስፍራ ከሚያልፍ አንድ ሺህ ዓመት ይሻላል፡፡ [84:10]

ጸሐፊው በክፉዎች ድንኳኖች ውስጥ ከመኖር ይልቅ በአምላኩ ቤት ውስጥ ምን መሆን ይመርጣል?

እርሱ በአምላኩ ቤት በር ጠባቂ መሆንን ይመርጣል፡፡ [84:10]