am_tq/mat/04/01.md

816 B

በዲያቢሎስ እንዲፈተን ኢየሱስን ወደ ምድረ በዳ የመራው ማን ነው?

በዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን ወደ ምድረበዳ መራው። [4:1]

ኢየሱስ በምድረ በዳ ለምን ያክል ጊዜ ጾመ?

ኢየሱስ በምድረ በዳ ለአርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ። [4:2]

ዲያቢሎስ ለኢየሱስ ያቀረበው የመጀመሪያው ፈተና ምን ነበር?

ዲያቢሎስ ኢየሱስ ድንጋዩን ወደ ዳቦ እንዲቀይር ፈተነው። [4:3]

ኢየሱስ ለመጀመሪያው ፈተና ምን መልስ ሰጠ?

ኢየሱስ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም አለ። [4:4]