28 lines
2.0 KiB
Markdown
28 lines
2.0 KiB
Markdown
# አጠቃላይ መረጃ፡-
|
|
|
|
ትይዩነት በዕብራውያን ግጥም ውስጥ የተለመደ ነው፡፡ (ግጥም እና ትይዩነት የሚለውን ይመልከቱ)
|
|
|
|
# የአሳፍ መዝሙር
|
|
|
|
“ይህ አሳፍ የጻፈው መዝሙር ነው፡፡” ይህ በ መዝሙረ ዳዊት 53:1 ላይ አንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት፡፡
|
|
|
|
# እኔ ግን እግሬ ሊሰናከል፣ አዳልጦኝም ልወድቅ ጥቂት ቀረኝ
|
|
|
|
ዘማሪው የሚናገረው እግዚአብሔርን መታመን አንዳልቻለና በሚያዳልጥ መንገድ ሲራመድ ሊወድቅ እንደደረሰ አድርጎ ራሱን በማሰብ ሀጢአት ለመስራት እንደፈለገ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ በእግዚአብሔር መታመን ለማቆም ደርሼ ነበር፤ በእርሱ ላይ ትልቅ ሀጢአት ለመስራትና በደለኛ ለመሆን ደርሼ ነበር” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
|
|
|
|
# በአመፀኞች ቀንቼ ነበር
|
|
|
|
“አመፀኞች ቀናሁባቸው” ወይም “አመፀኞች ሰዎች የነበራቸው መልካም ነገር እንዲኖራቸው አልፈልግም”
|
|
|
|
# አመፀኞች
|
|
|
|
“አመጸኞች” የሚለወ ቅፅል እንደ ስም ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አመፀኞች ሰዎች” (የስም ቅጽሎች የሚለውን ይመልከቱ)
|
|
|
|
# የክፉዎች ባለጠግነት
|
|
|
|
“ባለጠግነት” የሚለው ቃል እንደ ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ክፉዎች በጣም ብዙ መልካም ነገር እንዳላቸው አይቼ” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)
|
|
|
|
# ክፉዎች
|
|
|
|
“ክፉዎች” የሚለው ቅፅል እንደ የስም ሀረግ ሊተረጎም ይቸላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ክፉ ሰዎች” (የስም ቅጽሎች የሚለውን ይመልከቱ)
|