am_tn/rom/15/15.md

1016 B

በእግዚአብሔር የተሰጠኝ ጸጋ

ጳውሎስ ጸጋን እግዚአብሔር በአካል እንደሰጠው የሚዳሰስ ስጦታ እንደሆነ አድርጎ ይናገራል። ጳውሎስ ኢየሱስን ለመከተል ከመወሰኑ በፊት ብዙ አማኞችን ያሰቃየ ቢሆንም እግዚአብሔር ሐዋርያ እንዲሆን ሹሞታል። ይህን በገቢር/አድራጊ ቅርጽ መተርጎም ትችላለህ። (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)

የአሕዛብ መስዋዕት ተቀባይ ይሆን ዘንድ

ጳውሎስ ወንጌል የመስበክ ስራውን ልክ እርሱ ካህን እንደሆነና ለእግዚአብሔር መስዋዕትን እንደሚያቀርብ አድርጎ ይስለዋል። አማራጭ ትርጉም፡- “አሕዛብ እግዚአብሔርን ሲታዝዙ እርሱን እንዲያስደስቱት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)