am_tn/psa/078/001.md

1.8 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡-

ትይዩነት በዕብራውያን ግጥም ውስጥ የተለመደ ነው፡፡ (ግጥም እና ትይዩነት የሚለውን ይመልከቱ)

የአሳፍ ትምህርት

“ይህ አሳፍ የፃፈው ትምህርት ነው፡፡” “የአሳፍ ትምህርት” የሚለውን መዝሙረ ዳዊት 50:1 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት፡፡

ትምህርት

ይህ የሙዚቃ ስልትን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ በ መዝሙረ ዳዊት 32:1 ላይ እንዴት እንደተረጎምኸው ተመልከት፡፡

ትምህርቴን ስማ

“ትምህርት” የሚለው ስም በግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ የማስተምርህን ስማ” ወይም “ሳስተምርህ ስማ” (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

የአፌን ቃላቶች

“አፍ” የሚለው ቃል ሰውየውን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ቃሌን” (ወካይ የሚለውን ይመልከቱ)

አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ

“አፌን እከፍታለሁ” የሚለው ፈሊጥ መናገር ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “በምሳሌ እናገራለሁ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)

ስለ… ዘምሩ

“ተናገሩ፡፡” “ትናገራለች” የሚለውን በ መዝሙረ ዳዊት 19:2 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት፡፡

የተሰወሩ ነገሮችን

የአንተ ቋንቋ ሆን ተብሎ ለመረዳት አስቸጋሪ እንዲሆን የተደረጉትን አባባሎች የሚገልፅ ቃል ካለው እዚህ ላይ ልትጠቀምበት ትችላለህ፡፡