am_tn/psa/072/017.md

1.5 KiB

ስሙ ለዘላለም ፀንቶ ይኑር

ይህ አባባል ህዝቡ ሁልጊዜ እርሱን ለማሰብ ያላቸውን ፍላጎት በመግለፅ እግዚአብሔርን ለማክበር ጥቅም ላይ ውሏል፡፡አማራጭ ትርጉም፡- “ሰዎች ሁልጊዜ ስለ እርሱ ይወቁ” ወይም “ሰዎች እርሱ ማን እንደሆነ ፈፅሞ አይርሱ” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)

የእርሱ ስም

እዚህ ላይ “የእርሱ ስም” የሚለው የእግዚአብሔርን መልካም ስም የሚያመለክት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የንጉሱ ስም” ወይም “የንጉሱ መልካም ስም” ወይም “የንጉሱ ዝና” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)

ፀሀይ የምትኖረውን ዘመን ያህል

ግሱ ከዚህ በፊት ከነበረው ሀረግ ሊወሰድ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ፀሀይ ፀንታ የምትኖረውን ያህል” ወይም “ፀሀይ እስከበራች ድረስ” (አስጨምሬ የሚለውን ይመልከቱ)

ህዝቦች ሁሉ በእርሱ ይባረኩ

ይህ በገቢር ቅርጽ ሊብራራ ይችላል። አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር እርሱ ለህዝብ መልካም ነገርን እንዲፈፅም ያድርገው” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)

ብሩክ ነህ ይበለው

“እግዚአብሔር እንደባረከው ይወቅ”