am_tn/psa/037/031.md

1.4 KiB

የእግዚአብሔር ሕግ በልቡ አለ

እዚህ ጋ “በልቡ ውስጥ” የሚለው ሐረግ የሚያመለክተው ጥልቅ የሆነውን ውስጣዊ ማንነቱን ነው። አ.ት፡ “የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት በውስጣዊ ማንነቱ ውስጥ ያስቀምጠዋል” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

እግሮቹም አይንሸራተቱም

እዚህ ጋ እግዚአብሔርን ያለመታዘዝ ከትክከለኛው መንገድ መንሸራተትና መውደቅ እንደሆነ ተቆጥሮ ተነግሯል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር እንዲሄድበት በሚፈልገው መንገድ በሰላም ይሄዳል” ወይም “እግዚአብሔር እንዲያደርግ የፈለጋቸውን ነገሮች በሰላም ያደርጋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

አመጸኛው ሰው … ጻድቁን ሰው … ክፉው ሰው

እነዚህ ተለይተው የታወቁ ሰዎች አይደሉም። በጥቅሉ እንዲህ ዓይነቶቹን ሰዎች የሚያመለክቱ ናቸው። (See: Generic Noun Phrases)

ጻድቁን ሰው ይመለከተዋል

እዚህ ጋ መመልከት ጻድቅ የሆኑትን ሰዎች ለመጉዳት መከታተልን ያመለክታል። አ.ት፡ “ጻድቁን ሰው አድፍጦ ይጠብቀዋል” (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)