am_tn/pro/03/33.md

1.2 KiB

የእግዚአብሔር እርግማን በክፉዎች ቤት ላይ ነው

ፀሀፊው የእግዚአብሔርን እርግማን በክፉ ሰው ቤት ጫፍ ላይ እግዚአብሔር እንዳስቀመጠው ነገር እንደሆነ አድርጎ ይናገራል፡፡ “ቤት” የሚለው ቃል የቤተሰብ ምትክ ስም ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር የክፉ ሰውን ቤተሰብ ረግሟል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)

የፃድቃን ሰዎችን ቤት ይባርካል

“ቤት” የሚለው ቃል ቤተሰብን ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የፃድቅ ሰዎችን ቤተሰብ ይባርካል” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)

ለትሁታን ሞገሱን ይሰጣል

ፀሀፊው የእግዚአብሔርን ሞገስ እርሱ ለሰዎች የሚሰጠው ነገር እንደሆነ አድርጎ ይናገራል፡፡ አማራጭ ትረጉም፡- “ሞገሱን ለትሁት ሰዎት ያሳያል” ወይም “ለትሁት ሰዎች ጸጋውን ይሰጣል” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)