am_tn/pro/03/25.md

1.3 KiB

በክፉዎች አማካኝነት የሚደርስ ጥፋት፣ ሲመጣ

ይህ በገቢር/አድራጊ መልኩ ሊገለፅ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ክፉዎች ጥፋትን ሲያመጡ” (ገቢር/አድራጊ ወይም ተገብሮ/ተሳቢ የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ከጎንህ ይሆናል

“እግዚአብሔር ከአጠገብህ ይሆናል፡፡” አንድ ሰው ከሌላ ሰው ጎን መቆም የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር አንዱ ሰው ሌላኛውን ሰው ይረዳዋል እና ይደግፈዋል ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እግዚአብሔር ይደግፍሀል እና ይከራከርልሀል” (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)

እግርህ በወጥመድ እንዳይያዝ ይጠብቃል

ፀሀፊው “በሽብር” እና “በጥፋት” የተጎዳውን ሰው በወጥመድ እንደተያዘ አድርጎ ይናገራል፡፡ “እግር” የሚለው ቃል የሰውን ሁለንተና ይወክላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “አንተን ሊጎዱ ከሚፈልጉህ ሰዎች ይጠብቅሀል” (ተለዋጭ ዘይቤ እና ተዛምዶአዊ የሚለውን ይመልከቱ)