am_tn/num/32/04.md

2.5 KiB

አጠቃላይ መረጃ

ከሮቤልና ከጋድ የመጡ ሰዎች ለሙሴ፤ለአልዓዛርና ለሌሎቹ መሪዎች መናገራቸውን ይቀጥላሉ፡፡

እግዚአብሔር በእሥራኤል ማህበር ፊት የመታው ምድር

በዚያ ምድር የነበሩትን ሰዎች ድል እንዲያደርጓቸው እግዚአብሔር ችሎታውን የሰጣቸው ቢሆንም ልክ እግዚአብሔር ራሱ በእሥራኤላውያን ፊት ወጥቶ ጥቃት እንዳደረሰ ዓይነት ተድርጎ ተገልጿል፡፡“በዚያ የሚኖሩትን ሰዎች ድል እንደንነሳቻው እግዚአብሔር ችሎታውን ሰጠን” (ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ባሪያዎችህ

የሮቤልና የጋድ ሰዎች በዚህ መልክ ራሣቸውን የሚጠሩት ከፍ ያለ ሥልጣን ላለው ሰው አክበሮትን ለመሥጠት ነው፡፡

በዓይኖችህ ዘንድ ሞገስን አግኝተን እንደሆነ

እዚህ ላይ“ሞገስ” የሚለው ቃል ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን ተቀባይነትን ማግኘት ወይም መሪዎቹ በእነርሱ ደስ መሰኘታቸውን የሚያሣይ ነው፡፡እዚህ ላይ “ዓይኖች”የሚለው ቃል እይታ ለሚለው ቃል ገላጭ ሲሆን እይታ ደግሞ የማመዛዘን ችሎታውን የሚያመለክት ምሣሌያዊ አነጋገር ነው፡፡“በአንተ ዘንድ ሞገስን አግኝተን ከሆነ”ወይም “በእኛ ደስ የተሰኘህ ከሆነ”(ፈሊጣዊ አነጋገር፤ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃልንና ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ርስት አድርገህ ስጠን

ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡“ይህንን ምድር ለእኛ ስጠን”(ገቢራዊ ወይም ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)

ወደ ዮርዳኖስም ማዶ አታሻግረን

የፈለጉት ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ተሻግረው መሬት መጠየቅ ሣይሆን ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምሥራቅ በኩል የሚገኘውን ሥፍራ ነበር የፈለጉት፡፡“በዚያኛ በኩል ለእኛ መሬትን ለመሥጠት ብለህ የዮርዳኖስ ወንዝን እንድሻገር አታድርገን”(በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)