am_tn/num/30/08.md

2.2 KiB

ያደረገችው መሐላ…በችኮላ የተናገረችው ንግግር

“ያደረገችው መሐላ…ማለትም በችኮላ የተናገረችው ንግግር” እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች የሚያመለክቱት አንድን ነገር ነው፡፡ሁለተኛው ሐረግ ሴትዬዋ ያደረገችውን መሐላ የሚገልፅ ነው፡፡(ተመሳሳይነት የሚለውን ይመልከቱ)

የአንደበቷ ችኩል አነጋገር

“ችኩል አነጋገር”የሚለው ቃል የሚያመለክተው በችኮላ የገባችውን የተስፋ ቃል ነው፡፡እዚህ ላይ “አንደበቷ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው ራሷን ሴትዬዋን ነው፡፡አንደበቷ ከምትናገረው ነገር ጋር የተያያዘ በመሆኑ “አንደበቷ”በሚለው ቃል ተወክላለች፡፡“በችኮላ የተናገረቻቸው ነገሮች” ወይም“በችኮላ ቃል መግባቷ”(ነገርን በተለየ መንገድ መረዳት የሚለውን ይመልከቱ)

ራስዋን ያሰረችበትን

እዚህ ላይ ሙሴ አንዲት ሴት ቃል የገባቸውን ነገር ለመፈፀም ስትል የምታደርገውን መሠጠት ልክ ከሰውነቷ ጋር እንዳሰረችው ቁሣቁስ አድርጎ ነው የሚያቀርበው፡፡“ ረጋ ባለ መንፈስ ቃል የገባችውን ነገር ለመፈፀም የምታደርገው መሠጠት”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ነፃ ያወጣታል

እዚህ ላይ ሙሴ አንዲት ሴት ቃል የገባችውን ነገር ባትፈፅምም እግዚአብሔር ይቅር እንደሚላት ለመግለፅ ከታሰረችበት ነገር እንደምትለቀቅ ዓይነት አድርጎ አቅርቦታል፡፡የዚህ ዓረፍተ ነገር ሙሉ ሃሣብ የበለጠ ሊብራራ ይችላል፡፡“እግዚአብሔር ይቅር ይላታል” “የገባችውን ቃል ባትፈፅምም እግዚአብሔር ይቅር ይላታል”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውንና (በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ))