am_tn/num/30/06.md

2.6 KiB

በተረጋጋ መንፈስ ውስጥ ሆና ራስዋን ያሰረችበት መሐላ

እዚህ ላይ ሙሴ አንዲት ሴት ቃል የገባቸውን ነገር ለመፈፀም ስትል የምታደርገውን መሠጠት ልክ ከሰውነቷጋር እንዳሰረችው ቁሣቁስ አድርጎ ነው የሚያቀርበው፡፡“ ረጋ ባለ መንፈስ ቃል የገባችውን ነገር ለመፈፀም የምታደርገው መሠጠት”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ዝም ቢላት

እዚህ ላይ የሴትዋን ቃል ዝም ማለቱን ልክ አንድ ባለሥልጣን በሥልጣኑ እንደሚከለክላት ዓይነት ተደርጎ ተገልጿል፡፡(ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

የፀና አይሆንም

ይሄ ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን መሐላዋ የፀና እንደማይሆንና ተግባራዊ ማድረግ እንደማይጠበቅባት የሚያስረዳ ነው፡፡ይህንን ሐረግ በዘኁልቁ 30፡4 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡“ተግባራዊ እንድታደርገው አትገደድ”(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔርም ይቅር ይላታል

ይሄ የሚያመለክተው መሐላዋን ባትፈፀምም እንኳን እግዚአብሔር ይቅር ያላት መሆኑን ነው፡፡የዚህ ዓረፍተ ነገር ሙሉ ሃሣብ የበለጠ ሊብራራ ይችላል፡፡“መሐላዋን ባትፈፅምም እግዚአብሔር ይቅር ይላታል”(በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

በእነዚያ መሐላዎች ሥር ከሆነ

ይሄ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡መሐላዋ የፀና እንደማይሆንና ተግባራዊ ማድረግ እንደማይጠበቅባት የሚያስረዳ ነው፡፡ይህንን ሐረግ በዘኁልቁ 30፡4 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡“ተግባራዊ እንድታደርገው አትገደድ”(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በችኮላ

በአግባቡ ሳይታሰብ የሚደረግ ነገር፡፡

እነዚያ ግዴታዎች

“ግዴታዎች”የሚለው ቃል “ማስገደድ”በሚለው ሥም ሊገለፅ ይችላል፡፡“ራስዋን ግዴታዎች ውስጥ ያስገባችባቸው ነገሮች”(አሕፅሮተ ሥም የሚለውን ይመልከቱ)