am_tn/num/30/03.md

1.8 KiB

ራሷን በስእለት ብታስር

እዚህ ላይ ሙሴ አንዲት ሴት ቃል የመግባቷን ጉዳይ ልክ ራሷን በአንድነገር እንደምታስረው ዓይነት አድርጎ ነው ያቀረበው፡፡“የገባቸውን ቃል ለመፈፀም ራሷን ሰጠች”ወይም “አንድ ነገር ለመፈፀም ቃል ገባች”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

መሐላውና ቃል መግባቱ

እነዚህ ሁለቱ ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉም ነው ያላቸው፡፡አፅንኦት የሚሰጠው የገባችውን ቃል በሚመለከት ነው፡፡“መሐላው”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ራሷን ባሰረችበት

እዚህ ላይ ሙሴ አንዲት ሴት ቃል የገባቸውን ነገር ለመፈፀም ስትል የምታደርገውን መሠጠት ልክ ከሰውነቷጋር እንዳሰረችው ቁሣቁስ አድርጎ ነው የሚያቀርበው፡፡“የገባቸውን ቃል ለመፈፀም ራሷን ሰጠች”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ብታጥፍ

“ያለችውን ነገር ብትሰረዘው”

ስእለትዋ ሁሉ ይፀናል..መሐላ ሁሉ ይፀናል

እነዚህ ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ተመሳሳይ የሆነ ትርጉም ያላቸው ሲሆን መሐላዋን ሁሉ መጠበቅ እንዳለባት አፅነዖት የሚሰጥ ነው፡፡(ተመሳሳይነት የሚለውን ይመልከቱ)

ይፀናል

ይሄ ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን መሐላዋ የፀና እንደሆነና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባት የሚያስረዳ ነው፡፡“ተግባራዊ እንድታደርገው ትገደዳለች”(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)