am_tn/num/21/17.md

1.7 KiB

አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ

“ምንጭ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው በጉድጓድ ውስጥ ያለውን ውኃ ነው፡፡እሥራኤላውያን የሚያዳምጣቸው ሰው ይመስል ለውኃው የሚናገሩ ሲሆን ጉድጓዱን እንዲሞላላቸው ይጠይቁታል፡፡“አንተ ውኃ ጉድጓዱን ሙላ”(ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውንና ግዑዝ ነገሮች ሕይወት እንዳላቸው ተደርገው ሲገለፁ የሚለውን ይመልከቱ)

የሕዝብ አዛውንቶች ያጎደጎዱት፤አለቆችም የቆፈሩት

በመሠረቱ እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ የሆነ ትርጉም ያላቸው ሲሆን ውኃውን በመቆፈር ረገድ መሪዎች ያላቸውን ሚና አፅንኦት በመሥጠት ይናገራል፡፡(ተመሳሳይነት የሚለውን ይመልከቱ)

በበትረ መንግሥት፤በበትራቸውም

በትረመንግሥትየያዝየነበረውሥልጣንበነበራቸውሰዎችሲሆንበትርደግሞይያዝየነበረውበሁሉምሰውነበር፡፡እነዚህሁለቱለቁፋሮአገልግሎትየሚውሉመሣሪያዎችአይደሉም፡፡እነዚህሁለትቁሣቁሶች የሚያሣዩት በአካባቢያቸውየሚገኙትን ነገሮች ለመጠቀም ኩራት የሚባል ነገር የሌለባቸው ስለመሆኑ አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡“በትረ መንግሥታቸውንና በትራቸውን እንኳን ሳይቀር ይጠቀማሉ”(በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)