am_tn/num/20/14.md

1.1 KiB

ወንድምህ እሥራኤል

ሙሴ ይሄንን ሐረግ የተጠቀመበት ምክኒያት ዘሮቻቸው የሆኑት ያዕቆበና ኤሳው ወንድማማቾች ስለሆኑ እሥራኤላውንና ኤዶማውያን ዘመዳሞች እንደሆኑ አፅንዖት ለመስጠት ፈልጎ ነው፡፡

ወደ እግዚአብሔርም በጮሀን ጊዜ

“ዕርዳታ ያደርግልን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር በፀለይን ጊዜ”

ድምፃችንን ሰማ

እዚህ ላይ“ድምፅ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው መጮሃቸውንና ለእርሱ የተናገሩትን ነገር ነው፡፡“ጩኸታችንን አዳመጠ”ወይም “የጠየቅነውን ነገር ሰማን”(ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

እነሆ

“እነሆ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው ስላለፈው ነገር ማውራት ማቆማቸውንና አሁን ስላሉበት ሁኔታ እየተናገሩ መሆኑን ይገልፃል፡፡