am_tn/num/20/10.md

1.0 KiB

ከዚህ ድንጋይ ውኃ እናውጣላችሁን?

ሙሴ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው ከብስጭት የተነሣ ሲሆን ሕዝቡ በማጉረምረማቸው ሊገስፃቸው ነበር፡፡ይሄ እንደ መግለጫ ሊገለፅ ይችላል፡፡“ውኃ የለም ብላችሁ አጉረምርማችኋል፡፡እንደዚህ ከሆነ ከዚህ ዓለት ውኃ እናወጣላችኋለን”ወይም“ከዚህ ዓለት ውኃ ብናወጣላችሁ እንኳን ደስተኞች አትሆኑም፡፡ቢሆንም ግን አደርገዋለሁ”(ምላሽ የማያሻው ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

እኛ ማውጣት አለብን?

እዚህ ላይ“እኛ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሙሴንና አሮንን ሲሆን እግዚአብሔርንም የሚያካትት ሊሆን ይችላል፡፡ሆኖም ግን ሕዝቡን አያካትትም፡፡(“እኛ”የሚለውንና አካታችና አካታች ያልሆነውን የሚለውን ይመልከቱ)