am_tn/num/18/06.md

2.6 KiB

የዓረፍተ ነገር ማያያዣ

እግዚአብሔር ለአሮን መናገሩን ይቀጥላል፡፡

ለእናንተ ሥጦታ ናቸው

እግዚአብሔር ሌዋውያን አሮንን እንዲያግዙት የመደበበትን ሁኔታ እግዚአብሔር ለአሮን እንደተሰጠ ሥጦታ ዓይነት ተደርጎ ተገልጿል፡፡“ለአንተ እንደ ሥጦታ ናቸው”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ለእኔ የተሰጡ

ለእግዚአብሔር “የተሰጡ”የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ለማገልገል መለየታቸውን ነው፡፡ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡“ለራሴ የለየኋቸውን”ወይም“ለራሴ ለይቼያቸዋለሁ”(ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውንና ገቢራዊ ወይም ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)

አንተና የአንተ ልጆችህ ብቻ

እዚህ ላይ“አንተ”እና “የአንተ”የሚሉት ቃላት የነጠላ ቁጥር በመሆናቸው የሚያመለክቱት አሮንን ነው፡፡በሌሎች ሥፍራዎች ላይ “እናንተ”እና“የእናንተ”የሚሉት የብዙ ቁጥር በመሆናቸው የሚያመለክቱት አሮንንና ልጆቹን ነው፡፡(አንተ/እናንተ የሚለው ቃል በተለያየ መንገድ የሚገለፅበት የሚለውን ይመልከቱ)

ክህነታችሁን ጠብቁ

“የካህናትን ተግባር አከናውኑ”

በመጋረጃው ውስጥ ያለውን ሁሉ

በመጋረጃው ውስጥ የሚለው ቃል የሚያመለክተው ከመጋረጃው ጀርባ የሚገኘውን የውስጥ ክፍል ነው፡፡“ከመጋረጃው ጀርባ ባለው ከፍል ውስጥ የሚገኘውን ነገር ሁሉ”(ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

እንግዳ የሆነ ሰው ቢቀርብ ይገደል

ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡“ሌላ ሰው ቢቀርብ መገደል ይኖርበታል”ወይም “ሌላ ሰው ከቀረበ መግደል ይኖርባችኋል”(ገቢራዊ ወይም ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)

ቢቀርብ

ሊቀርቡት የማይገባቸው ነገር ምን እንደሆነ በግልፅ ሊብራራ ይችላል፡፡“ቅዱሱን ሥፍራ የሚቀርብ ሰው”(በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)