am_tn/num/10/35.md

1.9 KiB

ታቦቱ በተጓዘ ዘጊዜ

እዚህ ላይ ታቦቱ ልክ ሰው ይመስል ጉዞ እንደሚጓዝ ዓይነት ነው የሚገለፀው፡፡ታቦቱን የሚሸከሙ ሰዎች ነበሩ፡፡“ታቦቱ በተጓዘ ቁጥር ሰዎች ይሸከሙት ነበር፡፡”(ግዑዝ ነገሮች ሕይወት እንዳላቸው ተደርገው ሲገለፁ የሚለውን ይመልከቱ)

አቤቱ ተነሳ

እዚህ ላይ “ተነሳ”የሚለው ሐረግ እግዚአብሔር ሥራውን እንዲጀምር የሚጠየቅበት ሲሆን በዚህ አውድ ግን ሙሴ ጠላቶቻቸውን እንዲበትንላቸው እየለመነ ነው፡፡(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የሚጠሉህም ከፊትህ ይሸሹ

እዚህ ላይ ሙሴ ጠላቶቹ ከራሱ ከእግዚአብሔር የሚሸሹ ይመስል እግዚአብሔር ጠላቶቻቸውን ከእሥራኤል ሕዝብ እንዲሸሹ ምክኒያት እንዲሆንላቸው ነው የሚለምነው፡፡“አንተን የሚጠሉህን ከታቦትህና ከሕዝብህ እንዲሸሹ አድርጋቸው”(ምሣሌያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ታቦቱ ባረፈ ጊዜ

እዚህ ላይ ታቦቱ ሰው ይመስል እንደሚጓዝ ዓይነት ተደርጎ ነው የሚገለፀው፡፡ታቦቱን የሚሸከሙት ሰዎች ነበሩ፡፡“ሰዎች እንደተሸከሙት ታቦቱ ያርፍ ነበር”(ግዑዝ ነገሮች ሕይወት እንዳላቸው ተደርገው ሲገለፁ የሚለውን ይመልከቱ)

እልፍ አዕላፋት

ይሄ የሚያመለክተው የሰዎቹን ቁጥር ነው፡፡የዚህ ዓረፍተ ነገር ትርጉም የበለጠ ሊብራራ ይችላል፡፡“እልፍ አእላፋት ሕዝብ”(በግምት ላይ የተመሠረተ ዕውቀትና የተሟላ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)