am_tn/num/07/78.md

2.9 KiB

በአሥራ ሁለተኛውም ቀን

“ቀን 12”ወይም “ቀን ቁጥር 12” (ተከታታይነት ያለው ቁጥር የሚለውን ይመልከቱ)

የዔናን ልጅ አኪሬ

የዚህን ሰው ሥም በኦሪት ዘኁልቁ 1፡15 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡

130 ሰቅሎች የሚመዝን አንድ የብር ወጭት

አስፈላጊ ሆኖ የሚገኝ ከሆነ እነዚህ ሚዛኖች በዘመናዊ መለኪያዎች መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 7፡13 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡“አንድ የብር ወጭት አንድ ኪሎ ግራም ተኩል ገደማ ይመዝናል”ወይም “አንድ ብር ወጭት አንድ ኪሎ ግራም ከ 430 ግራሞች ይመዝናል”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለኪያና ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)

ሰባ ሰቅል የሚመዝን አንድ የብር ድስት

“አንድ የብር ድስት 70 ሰቅል ይመዝናል”አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ እነዚህ ሚዛኖች በዘመናዊ መለኪያዎች ሊፃፉ ይችላሉ፡፡ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 7፡13 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡”አንድ የብር ሣህን አንድ አሥራ ስምንተኛ ኪሎግራም ገደማ የሚመዝን ነው”ወይም “አንድ የብር ሣህን 770 ግራም ይመዝናል፡፡”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለከያ የሚለውን ይመልከቱ)

በቤተመቅደሱ የሰቅል ሚዛን መሠረት

የተለያዩ ዓይነት የሰቅል ሚዛኖች ነበሩ፡፡ይሄኛው ሰዎች በመቅደሱ ውስጥ ለሚገኘው የተቀደሰው ድንኳን ሰዎች የሚጠቀሙበት ነው፡፡“ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 7፡13 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡በመቅደሱ ውስጥ በሚገኘው የጥራት ደረጃ መሠረት የተመዘነ”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለከያ የሚለውን ይመልከቱ)

በዘይት የተለወሰ መልካም ዱቄት

ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡”በዘይት የተለወሰው መልካም ዱቄት”(ገቢራዊና ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)

አሥር ሰቅል የሚመዝን አንድ የወርቅ ሣህን

አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ይሄ በዘመናዊ መለኪያ ሊፃፍ ይችላል፡፡እነዚህን ተመሳሳይ የሆኑ ሚዛኖችን እንዴት በኦሪት ዘኁልቁ 7፡14 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመለከቱ፡፡”አንድ ወርቅ ሣህን አንድ አሥረኛ ኪሎግራም ይመዝናል”ወይም “አንድ የወርቅ ሣህን 110 ግራሞች ይመዝናል”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለከያ የሚለውን ይመልከቱ)