am_tn/num/07/18.md

2.4 KiB

በሁለተኛውም ቀን

“ቀን 2”ወይም “ቀን ቁጥር 2” (ተከታታይነት ያለው ቁጥር የሚለውን ይመልከቱ)

የሶገር ልጅ ናትናኤል

ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 1፡8 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡

130 ሰቅሎች የሚመዝን አንድ የብር ወጭት

አስፈላጊ ሆኖ የሚገኝ ከሆነ እነዚህ ሚዛኖች በዘመናዊ መለኪያዎች መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 7፡13 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡“አንድ የብር ወጭት አንድ ኪሎ ግራም ተኩል ገደማ ይመዝናል”ወይም “አንድ ብር ወጭት አንድ ኪሎ ግራም ከ430 ግራሞች ይመዝናሉል”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለኪያና ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)

ሰባ ሰቅል የሚመዝን አንድ የብር ድስት

“አንድ የብር ድስት 70 ሰቅል ይመዝናል”አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ እነዚህ ሚዛኖች በዘመናዊ መለኪያዎች ሊፃፉ ይችላል፡፡ይህንን በኦሪት ዘኁልቁ 1፡13 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡”አንድ የብር ሣህን አንድ አሥራ ስምንተኛ ኪሎግራም ገደማ የሚመዝን ነው”ወይም “አንድ የብር ሣህን 770 ግራም ይመዝናል፡፡”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለኪያና ቁጥሮች የሚለውን ይመልከቱ)

በቤተመቅደሱ የሰቅል ሚዛን መሠረት

የተለያዩ ዓይነት የሰቅል ሚዛኖች ነበሩ፡፡ይሄኛው በመቅደሱ ውስጥ ለሚገኘው የተቀደሰው ድንኳን ሰዎች የሚጠቀሙበት ነው፡፡ሚዛኖቹን ወደ ዘመናዊ መለኪያ እየለወጣችሁ ከሆነ ይሄንን ሐረግ የመተርጎሚያ ሌላ መንገድ እነሆ፡፡“በመቅደሱ ውስጥ በሚገኘው ደረጃ ሚዛን የተለካ”(መፅሐፍ ቅዱሣዊ መለከያ የሚለውን ይመልከቱ)

በዘይት የተለወሰ መልካም ዱቄት

ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡” በዘይት የተለወሰው መልካም ዱቄት”(ገቢራዊና ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)