am_tn/num/04/15.md

1.5 KiB

ቤተመቅደሱን መሸከም

እዚህ ላይ ቤተመቅደሱ የሚያመለክተው አሮንና ልጆቹ በልብሶችና በቆዳዎች የሸፈኗቸውን ዕቃዎች ሁሉ ነው፡፡“የቤተመቅደሱን ዕቃዎች ሁሉ መሸከም” (ነገርን በተለየ መንገድ መረዳት የሚለውን ይመልከቱ)

ከሠፈሩም ሲነሱ

እዚህ ላይ ሠፈር የሚለው ቃል የሚያመለክተው በሠፈሩ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ ነው፡፡“ሰዎች ወደፊት በሚጓዙበት ወቅት” (ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

ቀአት

የዚህን ሰው ሥም በኦሪት ዘኁልቁ 3፡17 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡

የመቅደሱን ዕቃዎች

“የተቀደሰውን ዕቃ”

ለብርሃኑ ዘይት

እዚህ ላይ “ብርሃን”የሚለው ቃል የሚያመለከተው “መብራትን”ነው፡፡“ለመብራቶቹ የሚያስፈልግ ዘይት” (ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

መጠበቅ

“መጠበቅ” የሚለው አሕፅሮተ ሥም እንደ ሥም(ሰዋሰው) ሊገለፅ ይችላል፡፡“የሚጠብቁት ሰዎች” (አሕፅሮተ ሥም የሚለውን ይመልከቱ)