am_tn/num/03/03.md

1.5 KiB

በክህነት የተቀቡና የተቀደሱት

ይሄ በድርጊት መልክ ሊገለፅ ይችላል፡፡“ሙሴ የቀባቸውና የቀደሳቸው” (ገቢራዊና ፍዝ የሚለውን ይመልከቱ)

ናዳብ…አብድዩ..ኢታምር

የእዚህን ሰዎች ሥም በኦሪት ዘኁልቁ 3፡2 ላይ እንዴት እንደተረጎማችሁት ተመልከቱ፡፡

በእግዚአብሔር ፊት ሞቱ

“ሞቱ”የሚለው ቃል በድንገት ሞቱ ለማለት ነው፡፡ “በእግዚአብሔር ፊት ድንገት ሞቱ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በእግዚአብሔር ፊት

ይሄ የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን መገኘት ነው፡፡ማለትም የሚከናወነውን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይመለከት ነበር ለማለት ነው፡፡“በእግዚአብሔር ህልውና ፊት” (ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)

ተቀባይነት የሌለውን እሣት አቀረቡ

እዚህ ላይ “እሣት”የሚለው ቃል “የሚቃጠል መሥዋዕት”የሚለውን ሃሣብ ለመግለፅ የዋለ ቃል ነው፡፡“እግዚአብሔር ያልተቀበለውን የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረቡ” (ከዋናው ሃሣብ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ለመግለፅ የሚውል ቃል የሚለውን ይመልከቱ)