am_tn/lev/26/18.md

1.6 KiB

ሰባት እጥፍ

እዚህ ሰባት እጥፍ በእርግጥ በቁጥሩ ልክ ማለት አይደለም እግዚአብሔር የቅጣቱን መጠን በፍጹም እንደሚጨምር ያመለክታል (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ትዕቢታችሁን እሠብራለሁ

እንዳይታበዩ ኃይልን መጠቀም ትዕቢታቸውን እንደመሥበር ተደርጐ ተነግሮአል:: አት: “ባላችሁ ጉልበት የማሰማችሁን ትዕቢት ለማቆም እቀጣችኋለሁ” ወይም “በጉልበታችሁ እንዳትታበዩ እቀጣችኋለሁ”:: (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሰማያችሁን እንደብረት ምድራችሁንም አንደናስ አደርጋለሁ

ይህም እግዚአብሔር ዝናብ እንዳይዘንብ ያደርጋል ማለት ነው:: ይህም ሰዎች ዘርን እንዳይዘሩ ወይም እህልን እንዳያመርቱ ምድሪቱን ያደርቃል ማለት ነው:: (see Simile)

ኃይላችሁ በከንቱ ያልቃል

እጅግ ብዙ መሥራት ኃይል እስኪያልቅ ድረስ ሙሉ ጉልበትን ተጠቅሞ መሥራት ተደርጐ ተገልጾአል:: “በከንቱ ያልቃል” የሚለው ሀረግ እጅግ ብዙ ቢሠሩም ምንም አያገኙም ማለት ነው አት በከንቱ እጅግ ብዙ ትሠራላችሁ ወይም እጅግ ብዙ ትሠራላችሁ ነገርግን ብዙ በሠራችሁት ምንም አታገኙም ዘይቤያዊ አገላለጽ ወይም ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ