am_tn/jos/01/01.md

2.1 KiB

ያህዌ

ይህ በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለህዝቡ ራሱን የገለጸበት ስም ነው፡፡ ይህንን እንዴት እንደሚተረጉሙት ስለ ያህዌ የቃል ትርጉም ገጽ/ጽሁፍን ይመልከቱ፡፡

ነዌ

የኢያሱ አባት (ስሞች እንዴት ይተረጎማሉ የሚለውን ይመልከቱ)

ይህንን ዮርዳኖስን አቋርጡ

"ማቋረጥ" ማለት "ከወንዙ ማዶ መሄድ/ወንዙን ማቋረጥ" ማለት ነው፡፡ "ከዚህ ዳርቻ ወደ ዮርዳኖስ ወዲያኛው ዳርቻ መሄድ/ማቋረጥ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣው አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

አንተ እና ይህ ህዝብ ሁሉ

"አንተ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢያሱን ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ቃል መገለጫ መልኮች ይመልከቱ)

ሁሉንም ስፍራ ሰጥቼሃለሁ

እግዚአብሔር ምድሪቱን በመጭው ጊዜ ለእስራኤል መስጠቱ የተገለጸው አስቀድሞ እንደሰጣቸው ተደርጎ ነው፡፡ ይህ ምድሪቱን በእርግጥ እንደሚሰጣቸው አጉልቶ ያሳያል፡፡ "ለእናንተ ሁሉንም ስፍራ እሰጣችኋለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የወደፊት ሃላፊ ጊዜ የሚለውን ይመልከቱ)

ለእናንተ ሰጥቻለሁ

"እናንተ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢያሱን እና የእስራኤል ህዝብን ሁለቱንም ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ቃል መገለጫ መልኮችን ይመልከቱ)

የእግራችሁ ጫማ የሚረግጠውን ስፍራ ሁሉ

ይህ የሚያመለክተው የዮርዳኖስን ወንዝ ሲያቋርጡ ኢያሱ እና እስራኤላውያን የሚጎዙበትን ስፍራ ሁሉ ነው፡፡ "በዚህ ምድር በምትሄዱበት ሁሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣው አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)