am_tn/job/41/16.md

1.3 KiB

አንዱ ወደ ሌላው እጅግ የቀረበ ነው

በአንዱ ረድፍ ሚገኙት ጋሻዎች ከሌላው ጋር እጅግ ቅርብ ነው፡፡ (ኢዮብ 41፡15)

የእነርሱ…እነርሱ

"የእነርሱ" እና "እነርሱ" የሚሉት ቃላት በመስመር የተደረደሩ ጋሻዎችን ያመለክታሉ፡፡ (ኢዮብ 41፡15)

ለየብቻ ሊለያዩ አይችሉም

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ማንም ሊገነጣጥላቸው አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

ከመደንፋቱ/ከማሽካካቱ

"ሲደነፈፋ/ሲያሽካካ፡፡" በመኝታ ከሚሰማ አጭር ማንኮራፋት ጋር ይመሳሰላል፡፡ ሊሰጥ የሚችለው ሌላ ትርጉም "ከማስነጠሱ ጋር" ወይም "ሲያስነጥስ" የሚል ነው፡፡

ዐይኖቹ የንጋት ሽፋሽፍትን ይመስላሉ

ይህ ማለት ዐይኖቹ የማለዳ ሰማይ እንደሚቀላ የቀሉ ናቸው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የእርሱ

"የእርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሌዋታንን ነው፡፡