am_tn/job/40/08.md

2.4 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

በእርግጥ እኔን ትክክል አይደለህም ትላለህን?

"በእርግጥ" የሚለው ቃል ኢዮብ እርሱን ትክክል አይደለህም በማለቱ መደነቁን እና በእርግጥም ይህን ለማለት መፈለጉን እንዲያረጋግጥ እየጠየቀው መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እኔን ትክክል አይደለህም በማለትህ ተገርሜያለሁ" ወይም "እኔን ትክክል አይደለህም ለማለት መፈለግህን እርግጠኛ መሆን አለብህ፣ ምክንያቱም እያልክ ያለኸው ያንን ነው፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ራስህን ትክክለኛ አድርገህ እኔን ትኮንናለህን?

ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ራስህን ንጹህ አድርገህ በመቁጠር እኔን መኮነን ትችላለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

የእግዚአብሔርን ክንድ የመሰለ

ክንድ የሚለው በክንድ ውስጥ ለሚገኝ ጥንካሬ ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "እንደ እግዚአብሔር ጥንካሬ ብርቱ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚውን ይመልከቱ)

እንደ እርሱ በድምጽ መብረቅ ታወጣለህ?

ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር በድምጹ እንደሚያርደው አንተ በእርግጥ በድምጽህ መብረቅ ማብረቅ አትችልም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)

እንደ እርሱ ድምጽ ያለ

"እርሱ በሚያደርግበት መንገድ እንዳለ ድምጽ" ወይም "እንደ እርሱ ድምጽ ያለ ድምጽ"