am_tn/job/40/01.md

1.3 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

ሁሉን ቻይ የሆነውን እንዲህ አድርግ ለማለት መድፈር የሚችል አለን?

ያህዌ ኢዮብን እየገሰጸው ነው፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ማንም ቢሆን እኔን ለመንቀፍ ወይም ከእኔ ጋር ለመከራከር መሞከር የለበትም፣ እኔ ሁሉን ቻይ አምላክ ነኝና፡፡" ወይም "አንተ ሰው ሆነህ ሳለ፣ ሁሉን ቻይ አምላክ የሆንኩትን እኔን ለመንቀፍ ትፈልጋለህ፤ ደግሞም እኔን ለማረም መሞከር የለብህም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ከእግዚአብሔር ጋር የሚከራከር፣ እርሱ ምላሽ ይስጥ

ያህዌ ስለ ራሱ እና ስለ ኢዮብ ሌሎች ሁለት ሰዎች እንደሆኑ እና በየትኛውም ስፍራ የሚገኝ ማንኛም ሰው ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር እንደሌለበት አድርጎ ይናገራል፡፡ "ከእኔ ጋር ትከራከራለህን፣ እንግዲያውስ መልስልኝ" (ተውላጠ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)