am_tn/job/39/21.md

1.5 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

እርሱ ይጎደፍራል/መሬቱን ይመታል

"እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ፈረስን ነው፡፡ ፈረሱ ምድርን በእግሩ ይመታል/ይጎደፍራል ምክንያቱም ምግያው እንዲጀምር በጣም ቸኩሏል፡፡ "በጉጉት መሬቱን ይመታል ደግሞም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

መጎድፈር

"በኮቴው መሬቱን መቆፈር/መምታት"

መሳሪያውን ለማግኘት

እዚህ ስፍራ "መሳሪያ" የሚለው የሚወክለው ለጦርነቱ የሚጠቀሙበትን ነው፡፡ "ወደ ጦርነት ለመግባት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በፍርሃት ላይ ያፌዛል

"በፍጹም አይፈራም"

ያፌዛል

"ይስቃል"

መጨነቅ

"ተስፋ መቁረጥ"

ወደ ኃላ አይመለስም

"አይሸሽም"

ኮሮጆ

ፍላጻዎችን መያዣ

ማስፈራራት

መርገፍገፍ እና ድምጽ ማሰማት

ሽንጥ

የፈረሱ ጎን

ጦር

ሰዎች በጠላቶቻቸው ላይ የሚወረውሩት ጫፉ ሹል የሆነ ብረት ያለው ረጅም በትር