am_tn/job/39/11.md

1.9 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

እዚህ ስፍራ ያህዌ ሶስት ጥያቄዎች የጠየቀው ኢዮብ እንደ ያህዌ እንዳልሆነ ክርክሩን ለመቀጠል ነው፤ ምክንየቱም ኢዮብ ጎሽን ሊቆጣጠር አይችልም፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ሀይሉ ታላቅ ስለሆነ እርሱን ትተማመናለህን?

ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ሀይሉ ታላቅ ስለሆነ በእርሱ ልትተማመን አትችልም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱን ታምናለህ

"እርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው "ጎሽ"ን ነው፡፡

ይሰራው ዘንድ ስራህን በእርሱ ላይ ትጥላለህ/ትተዋለህ?

ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ለአንተ ይሰራልህ ዘንድ ስራህን ለእርሱ መተው አትችልም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ይሰራልህ ዘንድ ስራህን ለእርሱ መተው

"ከባዱን ስራህን ይሰራልህ ዘንድ"

እህልህን ይወቃልህ/ያበራይልህ ዘንድ…በእርሱ ትታመናለህ?

እነዚህ ሁለት ሀረጎች በመሰረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ይይዛሉ፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እህልህን እንዲወቃልህ …በእርሱ ላይ ልትታመን አትችልም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ትይዩ ንጽጽራዊ ጥያቄ የሚሉትን ይመልከቱ)