am_tn/job/38/34.md

1.6 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ኢዮብን ሁለት ጥያቄዎችን የጠየቀው እርሱ እንጂ ኢዮብ የዝናብ ደመናዎችን እና መብረቅን እንደማይገዛ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

‘እኛ በዚህ አለን' …አንተ ልትነሳ ትችላለህ?

እነዚህ ጥያቄዎች በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎሙ ይችላሉ፡፡ "ብዙ የዝናብ ውሃ ይሸፍንህ ዘንድ ድምጽህን እሰከ ደመናት ድረስ ማሰማት ትችል እንደሆነ ንገረኝ፡፡ የመብረቅ ብልጭታን ይወጣ ዘንድ ልታዘው ትችል እንደሆነ ንገረኝ፤ እነርሱም ‘እዚህ አለን!' ይሉህ እንደሆነ ተናገር፡፡" በሚለው ውስጥ እንሚገኘ፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

ብዙ የዝናብ ውሃ

"ብዙ/የተትረፈረፈ" የሚለው ረቂቅ ስም "የበዛ" በሚል ቅጽል ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ብዙ የዝናብ ውሃ" ወይም "የውኆች ጎርፍ" በሚለው ውስጥ እንሚገኘ፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን መልከቱ)

እዚህ አለን

ይህ የሚያሳየው የመብረቅ ብልጭታዎች እንደ አገልጋይ ትዕዛዝ ለመቀበል ዝግጁ ነን ማለታቸውን ነው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)