am_tn/job/38/28.md

3.1 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ኢዮብን አራት ጥያቄዎችን የጠየቀው እርሱ እንጂ ኢዮብ ዝንብን እንደማያዘንብ፣ ጤዛና እና በረዶን እንደማይፈጥር እንደዚሁም አመዳይን እንደማያበጅ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

አጠቃላይ መረጃ፡

በእነዚህ ሶስት ስንኞች ውስጥ የሚገኙ እያንዳንዳቸው መስመሮች ተመሳሳይ ነገሮችን ይገልጻሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አጠቃላይ መረጃ፡

ዝናብ፣ ጤዛ፣ በረዶ፣ እና አመዳይ የተገለጹት እንደ ሰዎች እንደሚወለዱ ነው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ዝናብ አባት አለውን፣ ወይስ፣ የጤዛ ጠብታ አባቱ ማን ነው? በረዶ ከማን ማህጸን መጣ? የሰማይን ነጭ አመዳይ ማን ወለደው?

እነዚህ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊተረጎሙ ይችላሉ፡፡ "ዝናብ አባት እንዳለው፣ የዝናብ ጠብታዎችን ማን እንዳስገኘ ንገረኝ፡፡ በረዶ ከማን ማህጸን እንደወጣ፣ ደግሞም የሰማይን ነጭ አመዳይ ማን እንደወለደው ንገረኝ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

ለጤዛ ጠብታ አባቱ

ለጤዛ አባቱ የሆነው የሚለው ለመፈጠሩ ዘይቤያዊ አገላለጽ ነው፡፡ "የጤዛ ጠብታ እንዲኖር ምክንያት የሆነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በረዶ

"ቀዝቅዞ ጠጣር የሆነ/የረጋ ውሃ"

መውለድ

"ልጅ መስጠት"

ነጭ አመዳይ

በቅዝቃዜ መሬት ላይ በረዶ/ጠጣር የሆነ ጤዛ፣ ደማና በሌለበት ምሽቶች

ራሳቸውን የደበቁ እና እንደ ድንጋይ ጠጣር የሆኑ ውኆች

ውኆች የተገለጹት መደበቅ እንደሚችሉ ተደርጎ ነው፡፡ በክረምት በረዶ ከስሩ ውሃ ይደብቃል፡፡ (ሰውኛ እና ከባለቤቱ ጋር የሚጣቀስ ተውላጠ ስሞች የሚሉትን ይመልከቱ)

እንደ ድንጋይ ሆነ

የበረዶው ጠጣርነት የተገለጸው ድንጋይ እንደሆነ ተደርጎ ነው፡፡ "እንደ ድንጋይ ጠጣር/ጠንካራ ሆነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ጥልቁ

ይህ የሚያመለክተው ውሃው በጣም ጥልቅ የሆነን፣ ባህርን ወይም ውቅያኖስን ነው፡፡ "ጥልቁ ባህር" ወይም "የውቅያኖስ ጥልቀት" ወይም "ጥልቁ ውሃ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስማዊ ቅጽሎች የሚለውን ይምለከቱ)