am_tn/job/38/25.md

2.6 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ይህን ጥያቄ ኢዮብን የጠየቀው እርሱ እንጂ ኢዮብ ዝናብ እንዲዘንብ እና መብረቅ እንዲበርቅ እንደማያደርግ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

ለዝናብ መውረጃውን የሚፈጥርለት ወይም…ሳር እንዲበቅል የሚያደርገው ማን ነው?

ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊጻፈ ይችላል፡፡ "ለዝናብ መውረጃውን የማበጅለት፣ ሳር እንዲበቅል የማደርግ እኔ ብቻ ነኝ፣… እኔ ብቻ ይህንን አደርጋለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

የዝናብ መውረጃ

"የዝናብ ጎርፍ"

የመብረቅ መንገድ

"የመብረቅ ጉርምርምታ የሚሰማበት መንገድ"

ማንም ሰው በማይኖርበት መሬት፣ ማንም በማይኖርበት ምድረበዳ

እነዚህ ሁለት ሀረጎች ተቀራራቢ ትርጉም አላቸው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ማንም ሰው በማይኖርበት

"ሰዎች በሌሉበት"

ለማርካት

በውስጠ ታዋቂነት የቀረበው መረጃ ምድር ሳር እንድታበቅል የሚያደርገው ዝናብ ነው፡፡ "ስለዚህ ዝናብ ምድር እንድታበቅል ያደርጋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

አጠፋ ደግሞም አወደመ

"የፈራረሰ እና የተበላሸ፡፡" እነዚህ ሁለት ቃላት ተቀራራቢ ትርጉም አላቸው፤ ደግሞም የእነዚህን አካባቢዎች የፈራረሰ እና ባዶ ተፈጥሮ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ (ሄንዲየዲስ/ሁለት ቃላት ‘እና' በሚል አያያዥ ቃል የሚገኛኙበትና አንድን ጥልቅ ሀሳብ ለመግለጽ የሚያገለግል ዘይቤያዊ አነጋገር)

በሣር

"እየበቀለ ያለ ሣር" ወይም "በመብቀል ላይ የሚገኝ ሣር፡፡" ማደግ የጀመረ ይህ ሣር፡፡

ምድርን በአዲስ ሣር የሚሞላ

"ምድር አዲስ ሳር እንድታበቅል የሚያደርግ"