am_tn/job/38/16.md

1.7 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ አምስት ጥያቄዎችን የተጠቀመው እርሱ እንጂ ኢዮብ ምድርን እና ባህርን አለመፍጠሩን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

አጠቃላይ መረጃ፡

ቁጥር 16 እና 17 አያንዳንዳቸው ተመሳሳይ የሆነ ትርጉም ያላቸው ሀረጎችን ይዘዋል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

በስፋቷ… ሄደህባታል?

እነዚህ ጥያቄዎች አሉታዊ ምላሽ ይጠብቃሉ፡፡ ጥያቄዎቹ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊገለጹ ይችላሉ፡፡ "ወደ ባህር ውሃ መሰረት አልሁድክም፣ ወይም በጥልቁ ታችኛ ክፈል አልተራመድክም፡፡ የሞት ደጆች ለአንተ አልተገለጹም፤ ደግሞም የሞት ጥላ ደጆችን አላየህም፡፡ ምድርን በስፋቷ አላወቅካትም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

የውኆች መሰረትን/መገኛ

"ምንጮች"

ጥልቅ

ይህ ጥልቅ ውሃ የሚገኝበትን ባህርን ወይም ውቅያኖስን ያመለክታል፡፡ "ጥልቁ ባህር" ወይም "የውቅያኖስ ጥልቀት" ወይም "ጥልቁ ውሀ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስማዊ ቅጽል የሚለውን ይመልከቱ)

የሞት ደጆች ለአንተ ተገልጸውልሃል

x