am_tn/job/38/12.md

2.0 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ይህን ጥያቄ የተጠቀመው እርሱ እንጂ ኢዮብ ብርሃንን አለመፍጠሩን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

ክፉው ከእርሱ እንዲወገድ … አንተ ነቅንቀኸዋልን?

ይህ ጥያቄ አሉታዊ ምላሽ ይጠበቅበታል፡፡ ይህ በዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "አንተ ፈጽሞውኑ ክፉውን … ከእርሱ ነቅንቀህ አላስወገድክም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ለማለዳ ትዕዛዝ መስጠት

ያህዌ ማለዳ ትዕዛዝን መቀበል እንደሚችል እና እንደ ሰው ነገሮችን ማወቅ እንደሚችል ይናገራል፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይልከቱ)

ንጋት ስፍራውን እንዲያውቅ ማድረግ

"ንጋት ስፍራው የት እንደሆነ እንዲያውቅ ማድረግ"

ንጋት

በማለዳ ሰማይ ላይ ፀሐይ ከመውጣቷ አስቀድሞ የቀኑ ብርሃን መታየት

የምድርን ዳርቻ መያዝ

የንጋት ብርሃን የተገለጸው የምድርን አድማስ እንደያዘ ተደርጎ ነው፡፡ "የምድርን ዳርቻዎች መያዝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያው አነጋገር እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ክፉውን ከውስጧ ነቅንቆ ማስወገድ

የቀን ብርሃን የተገለጸው የማያስፈልጉ ነገሮች በመነቅነቅ እንደሚወገዱ ክፉ ሰዎችን እንደሚያስወግድ ተደርጎ ነው፡፡ "ክፉ ሰዎችን ከምድር ነቅንቆ ማስወገድ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያው አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)