am_tn/job/38/08.md

1.9 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ሌላ ጥያቄ የተጠቀመው እርሱ እንጂ ኢዮብ ምድርን አለመፍጠሩን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

በባህር ላይ በር የዘጋ ማን ነው… ደግሞስ ከባድ ጨለማን መጠቅለያው ያደረገለት ማን ነው?

ይህ በዐረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ማን በባህ ላይ በሮችን እንደዘጋበት ንገረኝ…ከባድ ጨለማንስ ማን መጠቅለያው እንዳደረገ ንገረኝ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

በባህር ላይ በሮችን የዘጋ

ያህዌ ባህር መላውን ምድር እንዳይሸፍን የከለከለበት መንገድ በባህሩ ላይ በር ከመዝጋት ጋር ተነጻጽሯል፡፡ "ውሃ ምድርን እንዳያጥለቀልቅ ከልክሏል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ከማህጸን የወጣ ይመስል

ያህዌ ባህርን የፈጠረበትን ሁኔታ ከልጅ መወለድ ጋር ያነጻጽረዋል፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ልብሱ

"ለባህር ልብስ ሆኖ"

ጥልቅ ጨለማ መጠቅለያው ሆኖ

"ጨለማ" የሚለው ረቂቅ ስም "ጨለመ" በሚል ቅጽል ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ከባድ ጨለማን መጠቅለያው አደረግሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

መጠቅለያ ጨርቅ/መጠምጠሚያ

ልጆች እንደተወለዱ የሚጠቀለሉበት ረጅም ቁራጭ ጨርቅ