am_tn/job/38/06.md

2.9 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ኢዮብን መገዳደሩን/መጠየቁን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

"የእርሷን" የሚለው ቃል መሬተን ያመለክታል፡፤

አጠቃላይ መረጃ፡

ያህዌ ታላቅነቱን ለማጉላት ብዙ ጥያቄዎችን ይጠቀማል፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

መሰረቷ የተጣለው በምን ላይ ነበር?

ይህ በዐረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ "መሰረቷ በምን ላይ እንደተጣለ ንገረኝ" (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

መሰረቷ የተጣለው በምን ላይ ነበር

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እኔ መሰረቷን በምን ላይ መሰረትኩ" (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

የእግዚአብሔር ልጆች በደስታ ሲጮኹ… በዚያን ጊዜ ማን ማዕዘኖቿን መሰረተ?

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ " የእግዚአብሔር ልጆች በደስታ ሲጮኹ… ያን ጊዜ ማን ማዕዘኖቿን እንደመሰረተ ንገረኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

የማለዳ ከዋክብት በአንድነት ሲዘምሩ ደግሞም የእግዚአብሔር ልጆች በደስታ ሲጮሁ

እነዚህ ሁለት መስመሮች በትርጉም ተመሳሳይ ናቸው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የማለዳ ከዋክብት በአንድነት ሲዘምሩ

የማለዳ ከዋክብት የተገለጹት ሰዎች እንደሚዘምሩ የሚዘምሩ ተደርገው ነው፡፡ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) በቀጣዩ መስመር እንደተገለጸው "የማለዳ ከዋክብት" ከ "እግዚአብሐር ልጆች" ጋር ተመሳሳይ ናቸው ወይም 2) "የማለዳ ከዋክብት" የሚለው የሚያመለክተው በሰማይ የሚገኙ ከዋክብትን ነው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የማለዳ ከዋክብት

"በማለዳ የሚያበሩ ደማቅ ከዋክብት"

የእግዚአብሔር ልጆች

ይህ የሚያመለክተው ሰማያዊ ፍጥረታት የሆኑተን መላዕክትን ነው፡፡ ይህ በኢዮብ 1፡6 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡

በደስታ ሰጮኹ

"ደስታ" የሚለው ረቂቅ ስም "ደስተኛነት" በሚል ተውሰከ ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "በደስተኝነት ጮኹ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

በደስታ

"በደስታ ተሞልተው ስለነበር"