am_tn/job/38/01.md

3.2 KiB

ከዚያም ያህዌ መናገር ጀመረ

እዚህ ስፍራ "ከዚያም" የሚለው ቃል የመጽሐፉን አዲስ ክፍል መጀመር ያሳያል፡፡ በእናንተ ቋንቋ አዲስ ትዕይንትን ለመጀመር ተመሳሳይ ቃል ካለ ያንን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡ "ያ ሁሉ ከሆነ በኋላ፣ ያህዌ መናገር ጀመረ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ለኢዮብ ተናገረ

"ለኢዮብ መለሰለት" ወይም "ለኢዮብ ምላሽ ሰጠው"

ያለ እውቀት በቃላት ጨለማን ወደ እቅድ የሚመለስ/የሚያመጣ እርሱ ማን ነው?

ያህዌ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመበት ኢዮብ ስለማያውቀው ነገር መናገሩን ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንተ ጨለማን ያለ እውቀት በቃላት አማካይነት ወደ እቅዴ አስገብተሃል/አምጥተሃ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን መልከቱ)

ይህን የሚያመጣ እርሱ ማን ነው

"ይህ ለማምጣት አንተ ማን ነህ"

ወደ እቅዶች ጨለማ የሚያመጣ

"እቅዴን የሚያበለሽ" ወይም "ተግባሬን ግራ የሚያጋባ፡፡" ኢዮብ የእግዚአብሔርን እቅድ እንዴት እንዳበላሸ የተገለጸው የእግዚአብሔርን እቅድ ለማየት ይበልጥ ከባድ እንዳደረገ ተደርጎ ነው፡፡ "ጨለማ" የሚለው ረቂቅ ስም "አጨለመ" በሚል ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እቅዶችን አጨለመ" ወይም "እቅዶች መታየት እንዳይችሉ ከባድ አደረገ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ረቂቅ ስሞች የሚሉትን ይመልከቱ)

ያለ እውቀት በቃላት አማካይነት

"ስለማታውቃቸው ነገሮች በመናገር"

ያለ እውቀት በመናገር

"እውቀት" የሚለው ረቂቅ ስም በቅጽል መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የማይታወቁ ቃላት" ወይም "እውቀት የሌለባቸው ቃላት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ

"ቀበቶህን እንደ ወንድ በወገብህ ዙሪያ እሰር፡፡" ወንዶች ከባድ ስራ ሲሰሩ በነጻነት እግራቸውን ማንቀሳቀስ እንዲችሉ በወገባቸው ዙሪያ ቀበቷቸውን ይታጠቃሉ፡፡ "እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ" የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር እንደ ስራ፣ ውድድር፣ ወይም ጦርነትን የመሰለ አንድ ነገር ለማድረግ ተዘጋጅ የሚል ትርጉም አለው፡፡ ኢዮብ ለእግዚአብሔር መልስ መስጠትን ለመሰለ ከባድ ስራ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ "ለከባድ ስራ ራስህን አዘጋጅ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)