am_tn/job/36/13.md

1.6 KiB

በልባቸው አምላክ የለሽ የሆኑ

እዚህ ስፍራ "ልብ" የሚለው የሚያመለክተው ሃሳብን እና ስሜትን ነው፡፡ ይህ ሀረግ ሰውየው እግዚአብሔርን ማመንን በግትርነት መቃወሙን ነው፡፡"በእግዚአብሔር ማመንን ማን ይቃወማል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር በአንድ ላይ በሚያስራቸው ጊዜ እንኳን

ኤሊሁ እግዚአብሔር ሰዎችን መቅጣቱን በገመድ እንደሚያስራቸው አድርጎ ይገልጸዋል፡፡ "እግዚአብሔር በሚቀጣች ጊዜ እንኳን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ህይወታቸው በቤተ ጣኦት አመንዝሮች መሃል ያከትማል

እዚህ ስፍራ "የቤተ ጣኦት አመንዝሮች" የሚለው የሚያመለክተው በጣኦት አምልኮ ቤተመቅደስ ውስጥ የሚያገለግሉ ወጣት ወንዶች የአምልኳቸው ክፍል አድርገው የሚፈጽሙትን ስነምግባር የሌለው ወሲባዊ ድርጊት ነው፡፡ ለዚህ ሀረግ ሊሰጡ የሚችሉ አማራጭ ትርጉሞች 1) አምላክ የለሾች ስነምግባር በሌለው ባህሪያቸው መሞታቸውን ወይም 2) አምላክ የለሾች በሀፍረት እና በውርደት ይሞታሉ፡፡