am_tn/job/36/10.md

1.8 KiB

እርሱ ጆሯቸውንም ደግሞ ይከፍታል

ኤሊሁ የሚናገረው የአንድን ሰው ጆሮ መክፈት ሰውየው እንዲሰማ ማድረግ መሆኑን ነው፡፡ "እርሱ እንዲሰሙም አድርጓል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በእርሱ ትዕዛዝ

"ትዕዛዝ" የሚለው ስም በግሳዊ ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እርሱ ለሚያዛቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ከክፋት መመለስ

ኤሊሁ አንድን ድርጊት ማቆም ከዚያ መመለስ አድርጎ ይናገራል፡፡ "ክፉ ከማድረግ መመለስ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቀኖቻቸውን በብልጽግና ይፈጽማሉ፣ አመቶቻቸውንም በእርካታ

"ቀናት" እና "አመታት" የሚሉት ቃላት ሁለቱም የሚያመለክቱት የአንድን ሰው የህይወት ዘመን ነው፡፡ "ዘመናቸውን/እድሜያቸውን በብልጽግና እና በእርካታ ይፈጽማሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

እነርሱ በሰይፍ ይጠፋሉ

ኤሊሁም የሚናገረው በሀይል በሰይፍ ስለሚጠፋ ሰው፣ በሰይፍ አንድ ሰው ስለገደላቸው ሰዎች ነው፡፡ "በአመጽ ይገደላሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)