am_tn/job/36/08.md

1.3 KiB

እነርሱ በሰንሰለት ቢታሰሩ እንኳን

እዚህ ስፍራ "እነርሱ" የሚለው የሚያመለክተው ኃጢአት ቢሰሩ እግዚአብሔር ለእርማት የሚቀጣቸውን ጻድቃን ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንዱ በሰንሰለት ቢያስራቸው" ወይም "አንዱ እስረኛ ቢያደርጋቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

በመከራ ገመድ ቢያጠምዳቸው

ኤሊሁ በስቃይ ውስጥ እንዲገባ የተደረገን ሰው የሚገልጸው፤ ያ ሰው በገመድ እንደተያዘ እና እንዲሰቃይ እንደተደረገ ነው፡፡ "አንዱ ሰው እነርሱ እንዲሰቃዩ አድርጓል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

የእነርሱ መተላለፍ እና የእነርሱ ኩራት

ግሱ ከቀደመው ሀረግ ሊገኝ ይችላል፡፡ "መተላለፋቸውን እና ኩራታቸውን ለእነርሱ ይገልጥላቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተዘለለ/የተተወ የሚለውን ይመልከቱ)